ከሆነ ዘመን በፊት ኖረን ያለፍነውን ህይወት እንደገና ልንኖር ስላልመጣን.. "ህይወት ይህች ናት!'' ብለን ስለ 'እንቅጩ' መናገር _ አንችልም። _ በቅጡ ካልገባን እና ካልተረዳነው ተፈጥሮ ጋር ስለምንኖር… ምንም ነገር ላይየተቋጨ ድምዳሜ መስጠት ይቸግረናል።
ዓለም በራሷና በሰሪዋ መንፈስ ለጠነከሩ …በሁለት ፅንፍ ተሞርደው ብሩህ ነገ ለሚታያቸው ተስፈኞች መልካም ፍሬን ትሰጣለች። ገንዘብ ሲኦል አያስገባም። ድሃ በመሆንም መንግስተ ሰማያት አይወረስም። እግዚአብሔር ለሁሉም ነፍስ ቸርነትን ያደርጋል። አንተ የሌለህን ስታስብ እሱ በሰጠክ መክሊት ያተረፍከውን ይጠብቃል። ሰው ስለሆንክ ሁል ጊዜ ከመለመን አትቦዝንም። ልብስ ስትለምነው ገላ እንደሰጠክ ትረሳለህ…….