የሰው ልጅ ስለ ዐለምና ስለ ራሱ፣ “ከየት መጣን?” ብሎ መጠየቅና ተገቢውን ምርመራ ማድረግ የሚገባ ነገር ነው። ሆኖም ግን ባለፉት ሁለት ምዕተ ዓመታት፤ ሰልጥኛለሁ የሚለው የሰው ልጅ የእግዚአብሔርን ሀልዎት ከመጠራጠር ጀምሮ ዐለምና በውስጧ ያለው ሁሉ የተገኘው በአጋጣሚ ዘገምተኛ ለውጥ (ኢቮሊዩሺን) ነው ከሚል ክህደት ላይ ደርሷል።
ለዚህ ደግሞ ዳርዊን ያመጣው ሳይንሳዊ የሚመስል የዝግመት ለውጥ መላ-ምት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ሳይንሳዊ ማስረጃዎቹ በተጨባች ሲታዩ ግን የዳርዊን ቲዎሪ እንደሚለው ሳይሆን ዐለምና በውስጧ ያለው ፍጥረት ሁሉ አዋቂ በሆነ ኃይል የተፈጠሩ መሆናቸውን የሚያሳዩ