"እሞታለሁ እንጂ ከዚህስ አልጠጣም'' ብዬ ጥዬዉ መጓዝ መጀመሬን እንጂ ሌላውን አላስታወሰም፡፡ ዳሩ ግን፣ራሴን ያገኘሁት የሞተ ውሻ ያለበት የገማ ውኃ ሲጠጣ ነበረ።ትዉልዴም፣እድገቴም ኢትዮዽያ ዉስጥ ነዉ። ሕልሜን ለመኖር የሕይወት ፈተናን ለማሸነፍ በብዙ የሞት ጎዳና መንገድ ተጉዣለሁ። በአሁኑ ሰዓት በሀገረ ጀርመን ለረጅም ዓመታት በመቆየት የሀገሪቱን ብሔራዊ ቋንቋ እንዲሁም የእጅ ሙያዎችን ተምሬያለሁ፡፡ በስደተኛ ካምፕ ውስጥ በሶሻል ስራ ላይ በመስራትና ከአባቴ ጋር ጥምርድርጅት መሰርተን ፣ የኢትዮጵያን ቡና እሴት በመጨመር ወደ ውጭ ሀገርበመላክ ላይ እገኛለሁ። ይህ እውነተኛ የህይወት ታሪክ መጽሐፍ ወቅቱን የጠበቀና አስተማሪ ሆኖ እንደሚያገለግል በማሰብ እነኾ ብያለሁኝ።
ናትናኤል መኩሪያ
***