“ይህን የመምህር ግርማን መጽሐፍ በርጋታና በጥሞና የሚያነብ ሰው ወደ እውነተኛው ሃይማኖተ ሰሚዕ (በትምህርት የሚገኝ ርቱዕ እምነት) መድረሱ አይቀሬ ነው። መጽሐፉ የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን የነገረ መለኮት ትምህርት መግቢያ እንዲኾን የተዘጋጀ ነውና። በርግጥም መጽሐፉ "እውነተኛ የበጎች በር እኔ ነኝ" ያለውን ጌታን መሠረት አድረጎ የትምህርቱም፣ የትርጓሜውም፣ የምሥጢሩ፣ የርቃቄው ኹሉ ምንጭ ጌታ መኾኑን አሥረግጦ የሚናገር ድንቅ በር ወይም መግቢያ ነው። በዚሁም ላይ ''ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጁ ሰፊ መንገዱ ትልቅ ነው" /ማቴ 7 ! 13/ ከተባለው ግምታዊ ነገረ መለኮት