አዳም የድህረ ዘመናዊ ልብወለድ መገለጫዎችን በስፋት በመጠቀም፤ በእውነታ በህይወት እና በልብወለድ መካከል ያሉ ጉዳዮችን በሂስ ለጥያቄ በማቅረብ በታሪክ እና በእውቀት መስክ አይነኬ የሆኑትን ጉዳዮች እንዲነኩ፡ የተሰቀሉ እንዲወርዱ እና እንዲጠየቁ፡ ከሌላ አቅጣጫ እንዲታዩ፣ በዚህ ውስጥም ማህበራዊ ህፀፆች ጎልተው እንዲወጡ በማድረግ ረገድ አዲሰ የልብወለድ አፃፃፍ ፈር ቀዷል፡፡ በኢትዮጵያ ስነፅሁፍ ታሪክም ሌላ ደማቅ አሻራ ጥሏል ወይም አኑሯል ማለት እችላለሁ፤